መዝሙር 125:1-3 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በእግዚአብሔር የሚታመኑ፣ሳትናወጥ ለዘላለም እንደምትኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው።

2. ተራሮች ኢየሩሳሌምን እንደ ከበቧት፣ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣ እግዚአብሔር በሕዝቡ ዙሪያ ነው።

3. ጻድቃን እጃቸውን፣ ለክፋት እንዳያነሡ፣የክፉዎች በትረ መንግሥት፣ለጻድቃን በተመደበች ምድር ላይ አያርፍም።

መዝሙር 125