20. እንዲህም አለ፤“ጥበብና ኀይል የእርሱ ነውና፣ የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ።
21. ጊዜንና ወቅትን ይለውጣል፤ነገሥታትን በዙፋን ያስቀምጣል፣ደግሞም ያወርዳቸዋል፤ጥበብን ለጠቢባን፣ዕውቀትንም ለሚያስተውሉ ይሰጣል።
22. የጠለቀውንና የተሰወረውን ነገር ይገልጣል፤በጨለማ ያለውን ያውቃል፤ብርሃንም ከእርሱ ጋር ይኖራል።
23. የአባቶቼ አምላክ ሆይ፤ አመሰግንሃለሁ፤አከብርሃለሁም፤ጥበብንና ኀይልን ሰጥተኸኛልና፤ከአንተ የጠየቅነውን ነገር አሳውቀኸኛል፤የንጉሡን ሕልም አሳውቀኸናል።”