ዘፍጥረት 46:6-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ከብቶቻቸውንና በከነዓን ምድር ያፈሩትን ሀብት ንብረታቸውን ይዘው፣ ያዕቆብና ዘሮቹ በሙሉ ወደ ግብፅ ወረዱ።

7. ወደ ግብፅም የወረደው፣ ወንዶች ልጆቹንና ወንዶች የልጅ ልጆቹን፣ ሴቶች ልጆቹንና ሴቶች የልጅ ልጆቹን ማለት ዘሮቹን ሁሉ ይዞ ነው።

8. ወደ ግብፅ የወረዱት የእስራኤል ልጆች፣ ያዕቆብ ዘሮቹ እነዚህ ናቸው፦የያዕቆብ የበኵር ልጅ ሮቤል።

9. የሮቤል ልጆች፦ሄኖኅ፣ ፈሉሶ፣ አስሮን እና ከርሚ ናቸው።

10. የስምዖን ልጆች፦ይሙኤል፣ ያሚን፣ ኦሃድ፣ ያኪን፣ጾሐርና ከከነዓናዊቷ ሴት የተወለደውሳኡል ናቸው።

ዘፍጥረት 46