16. በባዕዳን አማልክታቸው አስቀኑት፤በአስጸያፊ ጣዖቶቻቸውም አስቈጡት።
17. አምላክ ላልሆኑ አጋንንት፦ላላወቋቸው አማልክት፣ከጊዜ በኋላ ለተነሡ አማልክት፣አባቶቻችሁ ላልፈሯቸው አማልክት ሠዉ።
18. አባት የሆነህን ዐለት ከዳኸው፤የወለደህን አምላክ (ኤሎሂም) ረሳኸው።
19. እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን አይቶ ናቃቸው፤በወንድና በሴት ልጆቹ ተቈጥቶአልና።
20. እርሱም፣ “ፊቴን ከእነርሱ እሰውራለሁ፤”“መጨረሻቸው ምን እንደሚሆንም አያለሁ አለ፤ጠማማ ትውልድ፣የማይታመኑም ልጆች ናቸውና።