17. እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዲህ አለኝ፤
18. “የሞዓብ ዳርቻ ዔርን ዛሬውኑ ታልፋላችሁ።
19. ከየትኛውም የአሞናውያን ምድር ለእናንተ ርስት ስለማልሰጣችሁ፣ አሞናውያን ዘንድ በደረሳችሁ ጊዜ አታስቸግሯቸው፤ ለጦርነትም አታነሣሡአቸው። ያን ቦታ ርስት አድርጌ ለሎጥ ዘሮች ሰጥቻቸዋለሁ።”
20. ያም ደግሞ በዚያ ይኖሩ የነበሩት የረፋይማውያን ምድር እንደሆነ ይቈጠር ነበር፤ አሞናውያን ግን ዘምዙማውያን ብለው ይጠሯቸው ነበር።