ዘኁልቍ 6:22-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

22. እግዚአብሔርም (ያህዌ) ሙሴን አለው፤

23. “አሮንንና ልጆቹን እንዲህ በላቸው፤ ‘እስራኤላውያንን በምትባርኩበት ጊዜ እንዲህ በሉአቸው፤

24. “ ‘እግዚአብሔር (ያህዌ) ይባርክህ፤ይጠብቅህም፤

25. እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊቱን ያብራልህ፤ይራራልህም፤

26. እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊቱን ይመልስልህ፤ሰላሙንም ይስጥህ።’ ”

27. “በዚህ ሁኔታ ስሜን በእስራኤላውያን ላይ ያደርጋሉ፤ እኔም እባርካቸዋለሁ።”

ዘኁልቍ 6