ዘኁልቍ 26:20-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. የይሁዳ ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በሴሎም በኩል፣ የሴሎማውያን ጐሣ፤በፋሬስ በኩል፣ የፋሬሳውያን ጐሣ፤በዛራ በኩል፣ የዛራውያን ጐሣ፤

21. የፋሬስ ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በኤስሮም በኩል፣ የኤስሮማውያን ጐሣ፤በሐሙል በኩል፣ የሐሙላውያን ጐሣ፤

22. እነዚህ የይሁዳ ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት ሰባ ስድስት ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።

23. የይሳኮር ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በቶላ በኩል፣ የቶላውያን ጐሣ፣በፋዋ በኩል፣ የፋዋውያን ጐሣ፣

24. በያሱብ በኩል፣ የያሱባውያን ጐሣ፣በሺምሮን በኩል፣ የሺምሮናውያን ጐሣ፤

25. እነዚህ የይሳኮር ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት ሥልሳ አራት ሺህ ሦስት መቶ ነበሩ።

ዘኁልቍ 26