ኤርምያስ 6:4-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. “በእርሷ ላይ ጦርነት ዐውጁ፤ተነሡ በቀትር አደጋ እንጣልባት፤ወይ ጉድ! ቀኑ እኮ መሸብን!ጥላው ረዘመ።

5. እንግዲህ ተነሡ በሌሊት እናጥቃት፤ምሽጎቿንም እንደምስስ!”

6. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ዛፎቹን ቍረጡ፤በኢየሩሳሌም ዙሪያ የዐፈር ድልድል ሥሩ።ይህቺ ከተማ ቅጣት ይገባታል፤ግፍን ተሞልታለችና።

7. የውሃ ጒድጓድ ውሃ እንደሚያመነጭ፣እርሷም እንዲሁ ክፋቷን ታፈልቃለች።ዐመፅና ጥፋት በውስጧ ይስተጋባል፤ሕመሟና ቍስሏ ዘወትር ይታየኛል።

8. ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተጠንቀቂ፤አለበለዚያ ከአንቺ ዘወር እላለሁ፤ማንም ሊኖርባት እስከማይችል ድረስ፣ምድርሽን ባዶ አደርጋለሁ።”

9. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የወይን ፍሬ ተሟጦ እንደሚቃረም፣ከእስራኤል የተረፉትን እንዲሁ ይቃርሟቸው።ወይን ለቃሚ እንደሚለቅም፣እጅህን ወደ ቅርንጫፎቹ ደጋግመህ ዘርጋ።”

10. ለማን ልናገር? ማንን ላስጠንቅቅ?ማንስ ይሰማኛል?እነሆ፣ ጆሮዎቻቸው አልተገረዙምና፣መስማት አይችሉም። በእግዚአብሔር ቃል ይሣለቃሉ፤ደስም አይሰኙበትም።

ኤርምያስ 6