ኤርምያስ 5:6-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ስለዚህ አንበሳ ከዱር ወጥቶ ይሰባብራቸዋል፣የበረሓ ተኵላም ይቦጫጭቃቸዋል፤ብቅ የሚለውን ሰው ሁሉ ለመገነጣጠል፣ነብር በከተሞቻቸው ዙሪያ ያደባል፤ዐመፃቸው ታላቅ፣ክሕደታቸው ብዙ ነውና።

7. “ታዲያ፣ እንዴት ይቅር ልልሽ እችላለሁ?ልጆችሽ ትተውኛል፤እውነተኛውን አምላክ ትተው አማልክት ባልሆኑት ምለዋል፤እስኪጠግቡ ድረስ መገብኋቸው፤እነርሱ ግን አመነዘሩ፤ወደ ጋለሞቶችም ቤት ተንጋጉ።

8. እንደ ተቀለበ ብርቱ ድንጒላ ፈረስ ሆኑ፤እያንዳንዱም የሌላውን ሚስት ተከትሎ አሽካካ።

9. ስለ እነዚህ ነገሮች አልቀጣቸውምን?”ይላል እግዚአብሔር።“እኔ ራሴ እንደዚህ ዐይነቱን ሕዝብ፣አልበቀልምን?

10. “ወደ ወይን አትክልቷ ስፍራ ገብታችሁ አበላሹት፤ነገር ግን ፈጽማችሁ አታጥፉት፤ቅርንጫፎቿን ገነጣጥሉ፤ የእግዚአብሔር አይደሉምና፤

11. የእስራኤል ቤትና የይሁዳ ቤት፣ፈጽመው ከድተውኛል፤”ይላል እግዚአብሔር።

ኤርምያስ 5