ኤርምያስ 22:5-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ነገር ግን እነዚህን ትእዛዛት ባትጠብቁ፣ ይህ ቤተ መንግሥት እንዲወድም በራሴ ምያለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር።’ ”

6. ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት እንዲህ ይላል፤“አንተ ለእኔ እንደ ገለዓድ፣እንደ ሊባኖስ ተራራ ጫፍ ውብ ብትሆንም፣በርግጥ እንደ ምድረ በዳ፣ሰው እንደማይኖርባቸው ከተሞች አደርግሃለሁ።

7. በነፍስ ወከፍ መሣሪያ የሚይዙትን፣አጥፊዎችን በአንተ ላይ አዘጋጃለሁ።ምርጥ የዝግባ ዛፎችን ይቈርጣሉ፤ወደ እሳትም ይጥሏቸዋል።

8. “ከተለያየ አገር የመጡ ሕዝቦች በዚህች ከተማ በኩል ሲያልፉ፣ ‘እግዚአብሔር በዚህች ታላቅ ከተማ ላይ ለምን እንዲህ አደረገ?’ እያሉ እርስ በርስ ይነጋገራሉ፤

9. ከዚያም፣ ‘የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ኪዳን ትተው ሌሎችን አማልክት ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው’ ይላሉ።”

10. ከእንግዲህ ስለማይመለስ፣የተወለደባትንም ምድር ዳግመኛ ስለማያይ፣ለተማረከው ንጉሥ አምርራችሁ አልቅሱ እንጂ፣ቀድሞ ለሞተው አታልቅሱ፤ አትዘኑም።

11. በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤

ኤርምያስ 22