6. እንግዲህ ክርክሬን ስሙ፤የከንፈሬንም አቤቱታ አድምጡ።
7. ለእግዚአብሔር ብላችሁ በክፋት ትናገራላችሁን?ስለ እርሱስ በማታለል ታወራላችሁን?
8. ለእርሱ ታደላላችሁን?ለእግዚአብሔር ጥብቅና ልትቆሙ ነውን?
9. እርሱ ቢመረምራችሁ መልካም ነገር ይገኝባችኋልን?ሰውን እንደምታታልሉ፣ ልታታልሉት ትችላላችሁን?
10. በስውር አድልዎ ብታደርጉ፣በርግጥ እርሱ ይገሥጻችኋል።
11. ግርማው አያስደነግጣችሁምን?ክብሩስ አያስፈራችሁምን?