ኢሳይያስ 58:7-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ምግብህን ለተራበ እንድታካፍለው፣ተንከራታቹን ድኻ ወደ ቤትህ እንድታስገባው፣የተራቈተውን ስታይ እንድታለብሰው፣የሥጋ ዘመድህንም ፊት እንዳትነሣው አይደለምን?

8. ይህ ከሆነ ብርሃንህ እንደ ንጋት ጮራ ይፈነጥቃል፤ፈውስህ ፈጥኖ ይደርሳል፤ጽድቅህ ቀድሞህ ይሄዳል፤ የእግዚአብሔር ክብር ደጀን ይሆንልሃል።

9. የዚያን ጊዜ ትጣራለህ፤ እግዚአብሔርም ይመልስልሃል፤ለርዳታ ትጮኻለህ፤ እርሱም፣ ‘አለሁልህ’ ይልሃል።“የጭቈና ቀንበር፣የክፋትን ንግግርና ጣት መቀሰርን ከአንተ ብታርቅ፣

10. ለተራበው ብትራራለት፣የተገፉት እንዲጠግቡ ብታደርግ፣ብርሃንህ በጨለማ ያበራል፤ሌሊትህም እንደ ቀትር ፀሓይ ይሆናል።

ኢሳይያስ 58