33. “ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ አሦር ንጉሥ እንዲህ ይላል፤“ወደዚች ከተማ አይገባም፤ፍላጻ አይወረውርባትም፤ጋሻ አንግቦ አይመጣባትም፤በዐፈር ቍልልም አይከባትም።
34. በመጣበት መንገድ ይመለሳል፤ወደዚች ከተማም አይገባም”ይላል እግዚአብሔር።
35. “ስለ ራሴና፣ ስለ አገልጋዬም ስለ ዳዊት፣ይህችን ከተማ እጋርዳታለሁ፤ አድናታለሁም።”
36. ከዚያም የእግዚአብሔር መልአክ ወጣ፤ ከአሦራውያን ሰፈር አንድ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ሰው ገደለ፤ በሰፈር ያሉት ማለዳ ሲነሡ፤ ቦታው ሬሳ በሬሳ ነበር።
37. ስለዚህ የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም አመለጠ፤ ወደ ነነዌም ተመልሶ በዚያ ተቀመጠ።