7. እርሱ ግን በዚያ ቀን ድምፁን ከፍ አድርጎ፣“እኔ መፍትሔ አልሆንም፤በቤቴም ልብስና ምግብ የለኝም፤የሕዝብ መሪ አታድርጉኝ” ይላል።
8. ኢየሩሳሌም ተንገዳግዳለች፤ይሁዳም ለመውደቅ ተቃርባለች፤ንግግራቸውም ሆነ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚቃወም፣የክብሩንም መገኘት የሚያቃልል ነውና።
9. የፊታቸው ገጽታ ይመሰክርባቸዋል፤ኀጢአታቸውን እንደ ሰዶም በይፋ ይናገራሉ፤አይደብቁትምም፤ጥፋትን በራሳቸው ላይ ስላመጡ።ወዮላቸው!