12. አንተ የንጋት ልጅ፣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፤እንዴት ከሰማይ ወደቅአንተ ቀድሞ መንግሥታትን ያዋረድህ፤እንዴት ወደ ምድር ተጣልህ!
13. በልብህም እንዲህ አልህ፤“ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፤ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ አደርጋለሁ፤በተራራው መሰብሰቢያ፣በተቀደሰውም ተራራ ከፍታ ላይ በዙፋኔእቀመጣለሁ፤
14. ከደመናዎችም ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፤ራሴንም እንደ ልዑል አደርጋለሁ።”
15. ነገር ግን ወደ ሲኦል፣ወደ ጥልቁም ጒድጓድ ወርደሃል።