1. የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ባቢሎን ያየው ንግር፤
2. በተራቈተ ኰረብታ ዐናት ላይ ምልክት ስቀሉ፤ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ጩኹ፤በመሳፍንቱም በር እንዲገቡ፣በእጅ ምልክት ስጡ።
3. በድል አድራጊነቴ ደስ የሚላቸውን ቅዱሳኔን አዛለሁ፤ቍጣዬንም እንዲፈጽሙ፣ተዋጊዎቼን ጠርቻለሁ።
4. በተራሮች ላይ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ፣የሚሰማውን ጩኸት አድምጡበመንግሥታትም መካከል፣እንደ ተጨናነቀ ሕዝብ ድምፅ የሆነውን ውካታ ስሙ!የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርሰራዊቱን ለጦርነት አሰልፎአል።