ነህምያ 12:9-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ወንድሞቻቸው የሆኑት በቅቡቅያና ዑኒም በአገልግሎት ጊዜ ከእነርሱ ትይዩ ይቆሙ ነበር።

10. ኢያሱ ዮአቂምን ወለደ፤ ዮአቂም ኤልያሴብን ወለደ፤ ኤልያሴብ ዮአዳን ወለደ፤

11. ዮአዳ ዮናታንን ወለደ፤ ዮናታንም ያዱአን ወለደ።

12. በዮአቂም ዘመን የካህናቱ ቤተ ሰብ አለቆች እነዚህ ነበሩ፤ከሠራያ ቤተ ሰብ፣ ምራያ፤ከኤርምያስ፣ ሐናንያ፤

13. ከዕዝራ፣ ሜሱላም፤ከአማርያ፣ ይሆሐናን፤

14. ከሙሊኪ፣ ዮናታን፤ከሰብንያ፣ ዮሴፍ፤

15. ከካሪም፣ ዓድና፤ከመራዮት፣ ሔልቃይ፤

16. ከአዶ፣ ዘካርያስ፤ከጌንቶን፣ ሜሱላም፤

17. ከአብያ፣ ዝክሪ፤ከሚያሚንና ከሞዓድያ፣ ፈልጣይ፤

18. ከቢልጋ፣ ሳሙስ፤ከሸማያ፣ ዮናታን፤

19. ከዮያሪብ፣ መትናይ፤ከዮዳኤ፣ ኦዚ፤

20. ከሳላይ፣ ቃላይ፤ከዓሞቅ፣ ዔቤር፤

21. ከኬልቅያስ፣ ሐሸብያ፤ከዮዳኤ፣ ናትናኤል።

ነህምያ 12