6. ዳዊትም ጽድቅ ያለ ሥራ ስለሚቈጠርለት ሰው ብፅዕና እንዲህ ብሎአል፤
7. “መተላለፋቸው ይቅር የተባለላቸው፣ኀጢአታቸው የተሰረየላቸው፣ብፁዓን ናቸው።
8. ኀጢአቱን፣ ጌታ ከቶ የማይቈጥርበት ሰውብፁዕ ነው።”
9. ይህ ብፅዕና ለተገረዙት ብቻ ነው ወይስ ላልተገረዙትም? የአብርሃም እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት ብለናል።
10. ታዲያ እንዴት ተቈጠረለት? ከተገረዘ በኋላ ነው ወይስ ከመገረዙ በፊት? የተቈጠረለት ከተገረዘ በኋላ ሳይሆን ከመገረዙ በፊት ነው።