ምሳሌ 2:8-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. የፍትሕን መንገድ ይጠብቃል፤የታማኞቹንም አካሄድ ያጸናል።

9. በዚያን ጊዜ ጽድቅን፣ ፍትሕን፣ ሚዛናዊነትን፣መልካሙንም መንገድ ሁሉ ትገነዘባለህ፤

10. ጥበብ ልብህ ውስጥ ትገባለችና፤ዕውቀትም ነፍስህን ደስ ታሰኛለች፤

11. የመለየት ችሎታ ይጋርድሃል፤ማስተዋልም ይጠብቅሃል።

12. ጥበብ ንግግራቸው ጠማማ ከሆነ ሰዎች፣ከክፉዎችም መንገድ ታድንሃለች፤

13. እነዚህም በጨለማ መንገድ ለመሄድ፣ቀናውን ጐዳና የሚተዉ ናቸው፤

14. ክፉ በመሥራት ደስ የሚላቸው፣በክፋት ጐዳና ሐሤት የሚያደርጉ፣

15. መንገዳቸው ጠማማ፣በአካሄዳቸው ጠመዝማዞች ናቸው።

16. ከአመንዝራ ሴትም ትጠብቅሃለች፤በአንደበቷም ከምታታልል ዘልዛላ ታድንሃለች፤

17. ይህችም የልጅነት ባሏን የተወች፣በአምላኳ ፊት የገባችውን ኪዳን ያቃለለች ናት።

ምሳሌ 2