ምሳሌ 13:17-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. ክፉ መልእክተኛ መከራ ውስጥ ይገባል፤ታማኝ መልእክተኛ ግን ፈውስን ያመጣል።

18. ተግሣጽን የሚንቅ ወደ ድኽነትና ኀፍረት ይሄዳል፤ዕርምትን የሚቀበል ሁሉ ግን ይከበራል።

19. ምኞት ስትፈጸም ነፍስን ደስ ታሰኛለች፤ተላሎች ግን ከክፋት መራቅን ይጸየፋሉ።

ምሳሌ 13