1. እግዚአብሔር ነገሠ፤ሕዝቦች ይንቀጥቀጡ፤በኪሩቤል ላይ በዙፋን ተቀምጦአል፤ምድር ትናወጥ።
2. እግዚአብሔር በጽዮን ታላቅ ነው፤ከሕዝቦችም ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ብሎአል።
3. ታላቁንና አስፈሪውን ስምህን ይወድሱ፤እርሱ ቅዱስ ነው።
4. ፍትሕን የምትወድ፣ ኀያል ንጉሥ ሆይ፤አንተ ትክክለኝነትን መሠረትህ፤ፍትሕንና ቅንነትንም፣ለያዕቆብ አደረግህ።
5. አምላካችንን እግዚአብሔርን ከፍ ከፍ አድርጉት፤በእግሩ መርገጫ ስገዱ፤እርሱ ቅዱስ ነውና።