10. ሕዝቦች፣ “አምላካቸው የት አለ?”ለምን ይበሉ?የፈሰሰውን የአገልጋዮችህን ደም በቀል፣ዐይናችን እያየ ሕዝቦች ይወቁት።
11. የእስረኞች ሰቈቃ በፊትህ ይድረስ፤በክንድህም ብርታት፣ሞት የተፈረደባቸውን አድን።
12. ጌታ ሆይ፤ ጎረቤቶቻችን በአንተ ላይ የተዘባበቱትን መዘባበት፣ሰባት ዕጥፍ አድርገህ አስታቅፋቸው።
13. እኛ ሕዝብህ፣ የማሰማሪያህ በጎችህ፣ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለን፤ከትውልድ እስከ ትውልድም፣ውለታህን እንናገራለን።