18. ወደ ላይ ዐረግህ፤ምርኮ አጋበስህ፤ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ አንተ በዚያ ትኖር ዘንድ፣ከዐመፀኞችም ሳይቀር፣ከሰዎች ስጦታን ተቀበልህ።
19. ሸክማችንን በየዕለቱ የሚሸከምልን፣አዳኝ አምላካችን፣ ጌታ ይባረክ። ሴላ
20. አምላካችን የሚያድን አምላክ ነው፤ከሞት ማምለጥ የሚቻለውም በጌታ በእግዚአብሔር ነው።
21. በእርግጥ እግዚአብሔር የጠላቶቹን ራስ፣በኀጢአታቸውም የሚጸኑትን ሰዎች ጠጒራም አናት ይፈነካክታል።