መዝሙር 3:5-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁ፤ እግዚአብሔር ደግፎ ይዞኛልና እነቃለሁ።

6. በየአቅጣጫው የከበበኝን፣አእላፍ ሕዝብ አልፈራም።

7. እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ!አምላኬ ሆይ፤ ታደገኝ፤የጠላቶቼን ሁሉ መንጋጋ ትመታለህ፤የክፉዎችንም ጥርስ ትሰባብራለህ።

8. ማዳን የእግዚአብሔር ነው፤በረከትህ በሕዝብህ ላይ ይሁን። ሴላ

መዝሙር 3