2. ለርዳታ በጮኽሁ ጊዜ፣ወደ ቅዱስ ማደሪያህ፣እጆቼን በዘረጋሁ ጊዜ፣የልመናዬን ቃል ስማ።
3. በልባቸው ተንኰል እያለ፣ከባልንጀሮቻቸው ጋር በሰላም ከሚናገሩ፣ከክፉ አድራጊዎችና፣ከዐመፃ ሰዎች ጋር ጐትተህ አትውሰደኝ።
4. እንደ ሥራቸው፣እንደ ክፉ ተግባራቸው ክፈላቸው፤እንደ እጃቸው ሥራ ስጣቸው፤አጸፋውን መልስላቸው።
5. ለእግዚአብሔር ሥራ ግድ ስለሌላቸው፣ለእጆቹም ተግባራት ስፍራ ስላልሰጡ፣እርሱ ያፈርሳቸዋል፤መልሶም አይገነባቸውም።