ሉቃስ 1:52-65 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

52. ገዢዎችን ከዙፋናቸው አውርዶአቸዋል፤ትሑታንን ግን ከፍ ከፍ አድርጎአቸዋል፤

53. የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአቸዋል፤ሀብታሞችን ግን ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል፤

54. ምሕረቱን በማስታወስ፣ ባሪያውንእስራኤልን ረድቶአል፤

55. ይህም ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፣ለአብርሃምና ለዘሩ ያለውን ለዘላለም ለመጠበቅ ነው።”

56. ማርያምም ሦስት ወር ያህል ኤልሳቤጥ ዘንድ ከቈየች በኋላ ወደ ቤቷ ተመለሰች።

57. የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ቀን ደረሰ፤ ወንድ ልጅም ወለደች።

58. ጎረቤቶቿና ዘመ ዶቿም ጌታ ታላቅ ምሕረት እንዳደረገላት ሰሙ፤ የደስታዋም ተካፋዮች ሆኑ።

59. በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፤ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ፈለጉ፤

60. እናቱ ግን፣ “አይሆንም፤ ዮሐንስ መባል አለበት” አለች።

61. እነርሱም፣ “ከዘመዶችሽ በዚህ ስም የተጠራ ማንም የለም” አሏት።

62. አባቱንም ምን ስም ሊያወጣለት እንደሚፈልግ በምልክት ጠየቁት።

63. እርሱም መጻፊያ ሰሌዳ እንዲሰጡት ለምኖ፣ “ስሙ ዮሐንስ ነው” ብሎ ጻፈ፤ ሁሉም በነገሩ ተደነቁ።

64. ወዲያውም አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱ ተፈታ፤ እግዚአብሔርንም እያመሰገነ መናገር ጀመረ።

65. ጎረቤቶቹም ሁሉ በፍርሀት ተሞሉ፤ ይህም ሁሉ ነገር በደጋማው የይሁዳ ምድር ሁሉ ተወራ።

ሉቃስ 1