2 ዜና መዋዕል 8:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የራሱን ቤተ መንግሥት የሠራባቸው ሃያ ዓመት ከተፈጸመ በኋላ፣

2. ኪራም የሰጠውን ከተሞች አድሶ እስራኤላውያን እንዲሰፍሩባቸው አደረገ።

3. ከዚያም ሰሎሞን ወደ ሐማት ሱባ ዘመተ፤ ያዛትም።

4. በምድረ በዳውም ውስጥ ተድሞርንና ቀድሞ በሐማት ሠርቶአቸው የነበሩትን የዕቃ ቤት ከተሞች ሁሉ ሠራ።

2 ዜና መዋዕል 8