2 ነገሥት 9:18-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

18. ፈረሰኛውም ኢዩን ለመገናኘት ጋልቦ ሄደና፣ “ንጉሡ፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ብሎአል” አለው።ኢዩም፣ “ስለ ሰላም መጨነቅ የአንተ ጒዳይ አይደለም! ይልቅስ ወደ ኋላ እለፍና ተከተለኝ” አለው።ጠባቂውም፣ “መልእክተኛው ከእነርሱ ዘንድ ደርሶአል፤ ነገር ግን ተመልሶ አልመጣም” ብሎ አሳወቀ።

19. ስለዚህ ንጉሡ ሌላ ፈረሰኛ ላከ፤ ወደ እነርሱ ዘንድ እንደ ደረሰም፣ “ንጉሡ፣ ‘የመጣችሁት በሰላም ነውን?’ ይላል” አለው።ኢዩም “ስለ ሰላም መጨነቅ የአንተ ጒዳይ አይደለም! ይልቅስ ወደ ኋላ እለፍና ተከተለኝ” አለው።

20. ጠባቂው፣ “መልእክተኛው ከእነርሱ ዘንድ ደርሶአል፤ ነገር ግን ይህም ተመልሶ አልመጣም፤ የወታደሮቹ መሪ ሠረገላ አነዳዱ ልክ እንደ ናሜሲ ልጅ እንደ ኢዩ አነዳድ ነው፤ ሲነዳም እንደ እብድ ነው” ሲል አሳወቀ።

21. ኢዮራምም፣ “በሉ ሠረገላዬን አዘጋጁ” ብሎ አዘዘ። ሠረገላው እንደ ተዘጋጀም፣ የእስራኤል ንጉሥ ኢዮራምና የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ በየሠረገሎቻቸው ሆነው ኢዩን ለመገናኘት ሄዱ፤ የኢይዝራኤላዊው የናቡቴ ርስት በነበረው ዕርሻ ላይም ተገናኙት።

2 ነገሥት 9