1 ዜና መዋዕል 6:32-49 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

32. እነርሱም ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም እስኪሠራ ድረስ፣ በማደሪያው ይኸውም በመገናኛው ድንኳን ፊት ሆነው እየዘመሩ ያገለግሉ ነበር፤ አገልግሎታቸውንም የሚያከናውኑት በወጣላቸው ደንብ መሠረት ነው።

33. ከወንዶች ልጆቻቸው ጋር ሆነው ያገለገሉ ሰዎች እነዚህ ናቸው፤ከቀዓታውያን ልጆች፤ ዘማሪው ኤማን፣ የኢዮኤል ልጅ፣ የሳሙኤል ልጅ፣

34. የሕልቃና ልጅ፣ የይሮሐም ልጅ፣የኤሊኤል ልጅ፣ የቶዋ ልጅ

35. የሱፍ ልጅ፣ የሕልቃና ልጅ፣የመሐት ልጅ፣ የአማሢ ልጅ፣

36. የሕልቃና ልጅ፣ የኢዮኤል ልጅ፣የዓዛርያስ ልጅ፣ የሶፎንያስ ልጅ፣

37. የታሐት ልጅ፣ የአሴር ልጅ፣የአብያሳፍ ልጅ፣ የቆሬ ልጅ፣

38. የይስዓር ልጅ፣ የቀዓት ልጅ፣የሌዊ ልጅ፣ የእስራኤል ልጅ።

39. እንዲሁም የሔማን ወንድም አሳፍ በስተ ቀኙ ሆኖ ያገለግል ነበር፤አሳፍ የበራክያ ልጅ፣ የሳምዓ ልጅ፣

40. የሚካኤል ልጅ፣ የበዓሤያ ልጅ፣የመልክያ ልጅ፣

41. የኤትኒ ልጅ፣የዛራ ልጅ፣ የዓዳያ ልጅ፣

42. የኤታን ልጅ፣ የዛማት ልጅ፣የሰሜኢ ልጅ፣

43. የኢኤት ልጅ፣የጌድሶን ልጅ፣ የሌዊ ልጅ፤

44. በስተግራቸው በኩል አብረዋቸው ያሉት የሜራሪ ልጆች፤የቂሳ ልጅ ኤታን፣ የአብዲ ልጅ፣የማሎክ ልጅ፣

45. የሐሸብያ ልጅ፣የአሜስያስ ልጅ፣ የኬልቅያስ ልጅ፣

46. የአማሲ ልጅ፣ የባኒ ልጅ፣የሴሜር ልጅ፣

47. የሞሖሊ ልጅ፣የሙሲ ልጅ የሜራሪ ልጅ፣የሌዊ ልጅ፣

48. ሌዋውያን ወንድሞቻቸው ግን የእግዚአብሔርን ቤት የማደሪያ ድንኳን ተግባር እንዲያከናውኑ ተመድበው ነበር።

49. የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ባዘዘው መሠረት ስለ እስራኤል ማስተስረያ በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ የሚከናወነውን ተግባር ሁሉ፣ በመሠዊያው ላይ የሚቃጠል መሥዋዕትና በዕጣኑ መሠዊያ ላይ የሚቀርበውን መሥዋዕት የሚያቀርቡት ግን አሮንና ዘሮቹ ብቻ ነበሩ።

1 ዜና መዋዕል 6